የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • ዛሬ

ሐሙስ፣ ኅዳር 6

ለሁሉም ነገር አመስግኑ።—1 ተሰ. 5:18

ይሖዋን በጸሎት የምናመሰግንባቸው ብዙ ምክንያቶች አሉን። ስላገኘነው ስለ ማንኛውም መልካም ነገር ልናመሰግነው እንችላለን፤ ደግሞም የመልካም ስጦታ ሁሉ ምንጭ እሱ ነው። (ያዕ. 1:17) ለምሳሌ ምድራችን ስላላት ውበት እንዲሁም በተፈጥሮ ላይ ስለሚታየው ጥበብ ይሖዋን ልናመሰግነው እንችላለን። በተጨማሪም ስለ ሕይወታችን፣ ስለ ቤተሰቦቻችን፣ ስለ ወዳጆቻችን እና ስለ ተስፋችን ልናመሰግነው እንችላለን። ከዚህም ሌላ፣ ከእሱ ጋር ወዳጅነት የመመሥረት ውድ መብት ስለሰጠን ልናመሰግነው ይገባል። በግለሰብ ደረጃ ይሖዋን ለማመስገን የሚያነሳሱንን ምክንያቶች ለማሰብ ለየት ያለ ጥረት ማድረግ ሊያስፈልገን ይችላል። የምንኖረው ምስጋና ቢስ በሆነ ዓለም ውስጥ ነው። ሰዎች ብዙ ጊዜ የሚያተኩሩት ማግኘት በሚፈልጉት ነገር ላይ እንጂ ላሏቸው ነገሮች አመስጋኝነታቸውን ማሳየት በሚችሉበት መንገድ ላይ አይደለም። እንዲህ ያለው አመለካከት ከተጋባብን ጸሎታችን ልመና ብቻ ያካተተ ይሆንብናል። ይህ እንዲያጋጥመን ካልፈለግን ይሖዋ ላደረገልን ነገር በሙሉ አድናቆት ማዳበራችንን እና ማመስገናችንን መቀጠል አለብን።—ሉቃስ 6:45፤ w23.05 4 አን. 8-9

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ዓርብ፣ ኅዳር 7

ምንም ሳይጠራጠር በእምነት መለመኑን ይቀጥል።—ያዕ. 1:6

አፍቃሪ አባታችን ይሖዋ ስንሠቃይ ማየት አይፈልግም። (ኢሳ. 63:9) ያም ቢሆን እንደ ወንዝና ነበልባል ያሉ ፈተናዎች እንዳይደርሱብን አይከላከልልንም። (ኢሳ. 43:2) ነገር ግን በመካከላቸው ‘ለማለፍ’ እንደሚረዳን ቃል ገብቶልናል። እንዲሁም የሚደርስብን መከራ ዘላቂ ጉዳት እንዲያስከትልብን አይፈቅድም። ይሖዋ ኃያል ቅዱስ መንፈሱን በመስጠትም እንድንጸና ይረዳናል። (ሉቃስ 11:13፤ ፊልጵ. 4:13) በዚህም የተነሳ፣ ለመጽናትና ለእሱ ምንጊዜም ታማኝ ለመሆን የሚያስፈልገንን ማንኛውንም እርዳታ እንደሚሰጠን መተማመን እንችላለን። ይሖዋ እንድንተማመንበት ይጠብቅብናል። (ዕብ. 11:6) አንዳንድ ጊዜ የሚያጋጥመን መከራ ከአቅማችን በላይ እንደሆነ ይሰማን ይሆናል። እንዲያውም ይሖዋ የሚረዳን መሆኑን መጠራጠር ልንጀምር እንችላለን። ይሁንና መጽሐፍ ቅዱስ፣ በአምላክ ኃይል “ቅጥር መውጣት” እንደምንችል ያረጋግጥልናል። (መዝ. 18:29) በመሆኑም በጥርጣሬ ከመዋጥ ይልቅ ይሖዋ ጸሎታችንን እንደሚመልስልን በመተማመን በሙሉ እምነት ልንጸልይ ይገባል።—ያዕ. 1:6, 7፤ w23.11 22 አን. 8-9

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ቅዳሜ፣ ኅዳር 8

የፍቅር ወላፈን የእሳት ወላፈን ነው፤ የያህም ነበልባል ነው። ጎርፍ ፍቅርን ሊያጠፋው አይችልም፤ ወንዞችም ጠራርገው ሊወስዱት አይችሉም።—መኃ. 8:6, 7

ይህ ለእውነተኛ ፍቅር የተሰጠ እንዴት ያለ ግሩም መግለጫ ነው! እነዚህ ቃላት ለባለትዳሮች የሚያበረታታ ሐሳብ ይዘዋል፦ በመካከላችሁ የማይከስም ፍቅር ሊኖር ይችላል። ባለትዳሮች ዕድሜያቸውን በሙሉ የማይከስም ፍቅር ሊኖራቸው የሚችለው የበኩላቸውን ጥረት ካደረጉ ብቻ ነው። ለምሳሌ እሳት ያለማቋረጥ እንዲነድ ከተፈለገ ማገዶ ሊጨመርበት ይገባል። ማገዶ ካልተጨመረበት እሳቱ ቀስ በቀስ መጥፋቱ አይቀርም። በተመሳሳይም አንድ ባልና ሚስት ዕድሜያቸውን በሙሉ በመካከላቸው ጠንካራ ፍቅር ሊኖር ይችላል። ግን ይህ ሊሆን የሚችለው ጥምረታቸውን ለማጠናከር ጥረት ካደረጉ ብቻ ነው። አንዳንድ ጊዜ ባለትዳሮች በመካከላቸው ያለው ፍቅር እየቀዘቀዘ እንዳለ ሊሰማቸው ይችላል፤ በተለይም በኢኮኖሚ ችግር፣ በጤና እክል ወይም ልጆችን ማሳደግ በሚፈጥረው ውጥረት የተነሳ ጫና ሲበዛባቸው እንዲህ ሊሰማቸው ይችላል። ስለዚህ ‘የያህ ነበልባል’ እንዳይከስም ከተፈለገ ባሎችም ሆኑ ሚስቶች ከይሖዋ ጋር ያላቸውን ዝምድና ለማጠናከር ጥረት ማድረግ ያስፈልጋቸዋል። w23.05 20-21 አን. 1-3

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ